በዓለማችን ከኢትዮጵያ በስተቀር በድንበር ተሻጋሪ ወንዝ ላይ የወንዙ አመንጪ ሆና ግዘፍ ሁለገብ ግድብ የሌለው ሀገር የለም።

የአባይ ጉዳዩ ግድብ መገደብና በኢኮኖሚ መጠቀም ብቻ ሳይሆን ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳይም ጭምር ነው፡፡ እኛ ኢትዮጵያዊያን የሀገራችንን ሉዓላዊነት አሳልፈን የምንሰጥ ህዝቦች አይደለንም።

በዓለም አቀፍ የድንበር ተሻጋሪ ወንዝ ታሪክ የላይኛው የተፋሰስ ሀገር ሆኖ (upstream country) በተለይ የወንዙ መነሻ ሀገር በራሱ ሉአላዊ ድንበር ውስጥ በወንዙ ላይ ለምገነባው ማንኛውም ነገር ከኢትዮጵያ ውጭ በአስገዳጅነት ይህን ማድረግ አለብህ ይህን ማድረግ የለብህም የተባለ እስከዛሬ አንድም ሀገር የለም። በተቃራኒው በድንበር ተሻጋሪ ወንዝ ታሪክ የታችኛው የወንዙ ተፋሰስ ሀገር ሆኖ፣ ከላይኛው የተፋሰስ ሀገር የሚመጣውን ውሃ በበላይነት መጠቀም አለብኝ ወይም ይህን ያህል የውሃ መጠን ይገባናል ያለ ከግብፅ በስተቀር በዓለም ላይ የለም፣ ታይቶም አይታወቅም።

በዓለማችን ከ286 በላይ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ይገኛሉ። በእነዚህም ወንዞች ላይ በርካታ ግድቦች ተገንብተው አግልግሎት ባመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡ ነገር ግን በየትኛውም የሰው ልጅ ዘመን በኢትዮጵያ የአባይ ወንዝ ላይ የተፈፀመው እና እየተደረገ ያለው ተፅዕኖ በየትኛውም የድንበር ተሻጋሪ አህጉር/ሀገር አልተፈፀመም፤ የትኛውም የወንዙ መነሻ የላይኛው የተፋሰስ ሀገር እንደ ኢትዮጵያ የገዛ ወንዝን እንዳያለማ እና በወንዙ እንዳይጠቀም የተደረገ ወይም ጫና የተፈጠረበት ሀገር የለም።

በዓለማችን ከኢትዮጵያ በስተቀር በድንበር ተሻጋሪ ወንዝ ላይ ግዘፍ ሁለገብ ግድብ የሌለው ሀገር የለም። በየትኛውም የድንበር ተሻጋሪ ወንዝ ያላቸው ሀገራት ላይ ያልተፈፀመ ድርጊት ከድህነት ለመወጣት በምትጥረው ኢትዮጵያ ላይ አላስፈላጊ ተጽእኖ የሚደረግበት አንዳችም ምክንያት የለም።

በሀገራዊ፤አህጉራዊና አለማቀፋዊ ተሞክሮዎችን በማጣቀስ የናሽናል ኦይል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ታደሰ ጥላሁን በኢትዮጵያ ቴሌቪዝን ሰፊና በጥናት የተደገፍ ገለጻና ማብራሪያን ያካተተ ቃለ ምልልስ አድርገዋል፡

 

 

 

 

Tadesse Tilahun, National Oil Ethiopia PLC, CEO speaks about actions Taken to Combat COVID-19 by Ethiopia during the global Oil & Gas association for advancing environmental and social performance-IPIECA conference July 16, 2020”

 

IPIECA has held several regional sessions covering the Americas, Europe, and Australia, which have been attended by participants from around the globe, including the International Association of Oil & Gas Producers (IOGP), American Petroleum Institute (API), South African Petroleum Industry Association (SAPIA) and industry players like Schlumberger.

During this conference, Tadesse presents on “Actions Taken to Combat COVID-19 by Ethiopia" via video-conference during an Africa-focused session. He introduced the action taken to combat COVID-19 by Government, Private sectors, and financial institutions as the most excellent practice in Africa. Please read on for more details 

 

 

 

 

Dear our valued customer,
Please click the below calibration-list link to see the calibration information and you can search by Plate number to generate the required information.
 

 

Calibrations List New

 

 

ዓባይ ከግብጽ ይልቅ ለኢትዮጵያ የመኖርና ያለመኖር ምርጫ ነው“ አቶ ታደሰ ጥላሁን የኢትዮጵያ ነዳጅ ኩባንያዎች ማህበር ፕሬዚዳንት

 

አዲስ አበባ፡- ግብጽ 96 በመቶ የሃይል ምንጭ የምታገኘው ከተፈጥሮ ጋዝና ከነዳጅ ሲሆን በአንፃሩ ኢትዮጵያ 88 በመቶ የሃይል ምንጯ ደንን በመመጠር በመሆኑና ይህ ደግሞ በርሃማነትን ስለሚያስፋፋ ከግብጽ ይልቅ ለኢትዮጵያ ዓባይ የመኖርና ያለመኖር ምርጫ መሆኑን የኢትዮጵያ ነዳጅ ኩባንያዎች ማህበር ፕሬዚዳንት ገለፁ፡፡
የማህበሩ ፕሬዚዳንትና የኖክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ታደሰ ጥላሁን በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፤ የግብጽ ዋነኛ የሃይል ምንጯ በዓባይ ወንዝ ግድብ ሠርታ የምታመነጨው ሳይሆን ከተፈጥሮ ጋዝ (51 በመቶ)፣ ከነዳጅ (45 በመቶ)፣ ቀሪውን ከድንጋይ ከሰልና ከሌሎች የሃይል ምንጮች የምታገኘው ነው፡፡ በአንፃሩ 88 በመቶ ኢትዮጵያ ታዳሽ የሃይል ምንጭ ከእንጨትና ከእንስሳት ዕዳሪ (ባዮ ማስ) የሚገኝ በመሆኑ አሁንም አብዛኛው ህዝባችንና እናቶቻቸን ምግብ ለማብሰል ጫካን እየመነጠሩ ይጠቀማሉ፡፡ ይህ ደግሞ በአገራችን ድርቅን በማስፋፋት ከድህነት እንዳንወጣ ያደርገናል ብለዋል፡፡
ግብጽ ከውሃ የሚገኝ ሃይል በወሳኝነት የማያስፈልጋት መሆኑን ከሃይል አማራጭ ምንጮቿ መገንዘብ ያስፈልጋል ያሉት አቶ ታደሰ፤ ኢትዮጵያ ግን የሃይል ፍላጎቷን ከውሃ ማግኘት ካልቻላች ድህነትን ለማሸነፍ የያዘችው ግብግብ በፍፁም ሊሳካላት አይችልም ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ኢትዮጵያ እየገነባች ያለችው የህዳሴ ግድብ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ሃይል ለኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ሃይል ምንጭ ከመሆኑ ጎን ለጎን እናቶቻችንም ሆኑ እህቶቻችን ከአካባቢያቸው እርቀው ዛፍ እየቆረጡና ደን እየመነጠሩ የሚጠቀሙበትን ሁኔታ ያስቀራል፣ ግብርናውንም ለማዘመን ያግዛል ብለዋል፡፡
ግብጽ ለህዝቦቿ መቶ በመቶ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ያሳካች መሆኑን የጠቀሱት አቶ ታደሰ፣ በአንፃሩ
በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ገና 44 በመቶ ገደማ መሆናችንን ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ የእርሻ ኢኮኖሚና የሃይል ምንጭ ወደ ዘመናዊነት ካልተቀየረ የዓባይ ወንዝም ሆነ የተፋሰሶቹ ህልውና አደጋ ላይ እንደሚወድቅ ገልፀው የኢትዮጵያ የውሃ ምንጭ በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲመነጭ ዓባይም የሦስቱ አገራት ህዝቦች በአስተማማኝ ሁኔታ ላይ ጠቀሜታ እንዲውል በኢትዮጵያ ተራራና ሸንተረር የአካባቢ ጥበቃ ላይ ግብጽና ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ሆነው
ማልማትና መደገፍ ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ ግብጽ የዓባይ ውሃን ለመጠጥና ለመስኖ ልማት ብቸኛው አማራጫችን ነው የሚሉት ትርክት ሀሰት መሆኑን አውስተው ግብጽ ለአንድ ሺህ ዓመታት በላይ የሚያገለግላት ከፍተኛ የከርሰ ምድር ክምችት ያላት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
እንደ አቶ ታደሰ ገለፃ፤ ዓባይ ብቸኛው ድንበር ተሻጋሪ ወንዝ አይደለም፡፡ በዓለማችን 286 የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ይገኛሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ በአፍሪካ 63፣ በሰሜን
አሜሪካ 19፣ በደቡብ አሜሪካ 65፣ በእስያ 73፣ በአውሮፓ 66 ይገኛሉ፡፡ ለአብነት ያህል በአፍሪካ የሴኔጋል ተፋሰስ ከጊኒ አንስቶ ማሊን ሞሪታኒያንና ሴኔጋልን አቋርጦ አትላቲክ ውቂያኖስ የሚገባ ነው፡፡ ይህም በሁሉም የተፋሰሱ አገሮች በትብብር እየለማ ይገኛል፡፡ ለምሳሌ ሴኔጋል አንድ ማሊ አራት፣ ሞሪታኒያ ሁለት ጊኒ ሦስት ግድቦችን ገንብተውበታል፡፡
በዓለም ላይ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞች የተፋሰሱ አገሮች በስምምነት የሚያለሙበት ሁኔታ መኖሩን አውስተው ግብጽ አምስት ግድቦችን በዓባይ ላይ ሠርታ በእጅጉ እየተጠቀመችበት ትገኛለች፡፡ በአንፃሩ የዓባይ ወንዝ መነሻና ወንዙን አመንጪ የሆነችው ኢትዮጵያ አንድ ግድብ ዓባይ ላይ ስትገነባ ከመደገፍ ይልቅ መቃወሟ ጡት ነካሽ ያደርጋታል ብለዋል፡፡
ይሁን እንጂ ግብጾች የኢትዮጵያን ግድብ መቃወማቸው ለኢትዮጵያ ጥሩ ዕድል ነው፡፡ ምክንያቱም ይህንን ኢፍትሐዊ የሆነውን ድብቅ ሴራቸውን ለዓለም ህብረተሰብ ለመግለጽ አስችሏታልና ሲሉ አስረድተዋል፡፡
የዓለም ባንክ እ.ኤ.አ 2018 ባወጣው ጥናት በዓለም አቀፍ ደረጃ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ አለመሆን ዋነኛው የዕድገት እንቅፋት መሆኑን ለአገራት ምክረ ሀሳብ መስጠቱን አስታውሰው፤ ግብጾች በፈጠሩት የሀሰት ትርክት ምክንያት ባንኩ ለ92 አገሮች 500 በላይ ግድቦችን እንዲገነቡ ከ50 ቢሊዮን ዶላር በላይ ብድር ሲሰጥ ባንኩ የህዳሴ ግድብን መደገፍ ባለመቻሉ በኢትዮጵያዊያን እናቶች ከመቀነታቸው በአበረከቱት አስተዋጽኦ እየተገነባ የሚገኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
“በመጪው ሐምሌ ወር 2012 ዓ.ም መጀመሪያ ላይ ሙሌት መጀመሩ ለእኛ ኢትዮጵያዊያን ትልቅ ደስታና ፍሬውን ለማጣጣም መቃረባችን ማሳያ ነው“ ሲሉ የተናሩት አቶ ታደሰ፤ በያዝነው የክረምት ወቅትም ሁሉም ዜጋ ችግኝ በመትክልና በመንከባከብ ለአገራችን ዘላቂ ልማትና ዕድገት የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡
አዲስ ዘመን ሰኔ 19/2012
ጌትነት ምህረቴ

 

 

Export-business

Export Business is one of the divisions established recently. It is in charge of supplying Agro commodities to our valued customers around the globe. We export premium quality oil seeds and pulses to our customers destined in China, Middle East, Europe, Asia, etc.  Our focus is to offer premier quality products at the most competitive prices, thus ensuring our customers’ expectations are fully satisfied.

We are striving to be the leading supplier of Ethiopian agro commodities all around the world.

NOC is characterized by the following strengths:

  • Strong financial capacity.
  • Well organized logistics team.
  • Timely delivery of products per shipment schedule.
  • Highly experienced management team.
  • Leading market positions with excellent reputation in the country.

Products and Services

 

 

Station Locator

Quick Contact

National Oil Ethiopia Plc
Airport Road Street
Addis Ababa, Ethiopia
Tel: +251116639494
Fax: +251116639495
P. O. Box: 951 code 1250
Email: info@noc.com.et

www.nocethiopia.com

Connect with us